Telegram Group & Telegram Channel
ጥያቄ :- ሰላም እንዴት ናችሁ?
ጥያቄ ለመጠየቅ ነበር መናፍቃን እኛ ኦርቶዶክሳውያንን አንዲት ጥምቀት ተብሎ ተጽፎ ለምን በየዓመቱ ትጠመቃላችሁ? ብለው ይጠይቃሉ ቢያብራሩልን።

መልስ

👉 ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሚለው መጽሐፋቸው የዚህን ጥያቄ መነሻና ምላሹን እንዲህ ብለው ጽፈዋል። "የጠበሉን መረጨት አይተው በቀድሞ ዘመን ወደ ሀገራችን መጥተው የነበሩ ኢየሱሳውያን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ታጠምቃለች ብለው ጽፈዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ይህን የምትፈጽመው ጌታችን ለእኛ ብሎ ያሳየውን ትህትና ለመመስከር ለምዕመናን በረከተ ጥምቀትን ለማሳተፍ እንጂ የተጠመቁትን ምዕመናን እየመላለሰች በየዓመቱ አታጠምቅም። ጥምቀት አሐቲ [አንዲት] መሆኗን ታውቃለችና። [የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ.126]

ዲያቆን ብርሃኑ አድማስም በዓላት በሚለው መጽሐፉ በጥምቀት የምንጠመቀው ለሥርየተ ኃጢአት ጭምር መሆኑን ሲገልጽ እንዲህ ብሎአል።   "የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያንም  ለዚሁ አንጽሖተ ማይ (ውሃውን ለመቀደስ) እና ምእመናኑም በጥምቀት (በልጅነት) የቀደመ ኃጢአታቸው የተሠረየላቸውን ያህል በዚህ ዕለትም የሠሩት ኃጢአት ይሠረይላቸዋል ትላለች። [በዓላት፤ ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ገጽ ገጽ.71] ስለዚህም በረከተ ጥምቀቱን ለምዕመናን በማድረስ ማሳተፍና ሥርየተ ኃጢአትን መስጠት እንጂ  መላልሶ ማጥመቅ አይደለም። ልጅነት አንድ ጊዜ ብቻ ነውና።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት። ኤፌ.{ 4:5። ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት አትደገምም። በጸሎተ ሐይማኖት ላይም "ኃጢአት በሚሰረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን" ይላል።  ጥምቀት ከምናከብራቸው ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ጌታችን በቅዱስ ዮሐንስ ሊጠመቅ መሄዱን የምናስብበት በዓል ነው ከጌታችን ጥምቀትም በረከትን የምንሳተፍበት በዓል ነው። ጥምቀት ሊደገም ይቅርና ይህን የጌታን ጥምቀትን በማሰብ የምናከብረውን በዓል ለማክበር መብቱ እንኳ ያላቸው ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ በጥምቀት የሥላሴ ልጅነትን ያገኙ ክርስቲያኖች ናቸው። ስለዚህ በረከተ ጥምቀትን ለመሳተፍ እንጂ ልጅነት የምታሰጠዋ ጥምቀት የምትደገም ሆና አይደለም።

ጌታችን በወንጌል " የክርስቶስ ስለ ሆናችሁ በስሜ ጽዋ ውኃ የሚያጠጣችሁ ሁሉ፥ ዋጋው እንዳይጠፋበት እውነት እላችኋለሁ።" ማር.9:41 እንደተናገረ ስሙን አስበን የምናደርጋቸው የምንዘክራቸው የጌታን ዓበይትና ንዑሳን በዓላትን ማሰብ መዘከር ስለ እርሱም ብሎ ነዳያንን በምሕረት መጎብኘት ዋጋ የማያሳጣ ተግባር ነው።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]



tg-me.com/mnenteyiklo/2821
Create:
Last Update:

ጥያቄ :- ሰላም እንዴት ናችሁ?
ጥያቄ ለመጠየቅ ነበር መናፍቃን እኛ ኦርቶዶክሳውያንን አንዲት ጥምቀት ተብሎ ተጽፎ ለምን በየዓመቱ ትጠመቃላችሁ? ብለው ይጠይቃሉ ቢያብራሩልን።

መልስ

👉 ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሚለው መጽሐፋቸው የዚህን ጥያቄ መነሻና ምላሹን እንዲህ ብለው ጽፈዋል። "የጠበሉን መረጨት አይተው በቀድሞ ዘመን ወደ ሀገራችን መጥተው የነበሩ ኢየሱሳውያን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ታጠምቃለች ብለው ጽፈዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ይህን የምትፈጽመው ጌታችን ለእኛ ብሎ ያሳየውን ትህትና ለመመስከር ለምዕመናን በረከተ ጥምቀትን ለማሳተፍ እንጂ የተጠመቁትን ምዕመናን እየመላለሰች በየዓመቱ አታጠምቅም። ጥምቀት አሐቲ [አንዲት] መሆኗን ታውቃለችና። [የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ.126]

ዲያቆን ብርሃኑ አድማስም በዓላት በሚለው መጽሐፉ በጥምቀት የምንጠመቀው ለሥርየተ ኃጢአት ጭምር መሆኑን ሲገልጽ እንዲህ ብሎአል።   "የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያንም  ለዚሁ አንጽሖተ ማይ (ውሃውን ለመቀደስ) እና ምእመናኑም በጥምቀት (በልጅነት) የቀደመ ኃጢአታቸው የተሠረየላቸውን ያህል በዚህ ዕለትም የሠሩት ኃጢአት ይሠረይላቸዋል ትላለች። [በዓላት፤ ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ገጽ ገጽ.71] ስለዚህም በረከተ ጥምቀቱን ለምዕመናን በማድረስ ማሳተፍና ሥርየተ ኃጢአትን መስጠት እንጂ  መላልሶ ማጥመቅ አይደለም። ልጅነት አንድ ጊዜ ብቻ ነውና።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት። ኤፌ.{ 4:5። ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት አትደገምም። በጸሎተ ሐይማኖት ላይም "ኃጢአት በሚሰረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን" ይላል።  ጥምቀት ከምናከብራቸው ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ጌታችን በቅዱስ ዮሐንስ ሊጠመቅ መሄዱን የምናስብበት በዓል ነው ከጌታችን ጥምቀትም በረከትን የምንሳተፍበት በዓል ነው። ጥምቀት ሊደገም ይቅርና ይህን የጌታን ጥምቀትን በማሰብ የምናከብረውን በዓል ለማክበር መብቱ እንኳ ያላቸው ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ በጥምቀት የሥላሴ ልጅነትን ያገኙ ክርስቲያኖች ናቸው። ስለዚህ በረከተ ጥምቀትን ለመሳተፍ እንጂ ልጅነት የምታሰጠዋ ጥምቀት የምትደገም ሆና አይደለም።

ጌታችን በወንጌል " የክርስቶስ ስለ ሆናችሁ በስሜ ጽዋ ውኃ የሚያጠጣችሁ ሁሉ፥ ዋጋው እንዳይጠፋበት እውነት እላችኋለሁ።" ማር.9:41 እንደተናገረ ስሙን አስበን የምናደርጋቸው የምንዘክራቸው የጌታን ዓበይትና ንዑሳን በዓላትን ማሰብ መዘከር ስለ እርሱም ብሎ ነዳያንን በምሕረት መጎብኘት ዋጋ የማያሳጣ ተግባር ነው።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

BY ምን እንጠይቅሎ?


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2821

View MORE
Open in Telegram


ምን እንጠይቅሎ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram today rolling out an update which brings with it several new features.The update also adds interactive emoji. When you send one of the select animated emoji in chat, you can now tap on it to initiate a full screen animation. The update also adds interactive emoji. When you send one of the select animated emoji in chat, you can now tap on it to initiate a full screen animation. This is then visible to you or anyone else who's also present in chat at the moment. The animations are also accompanied by vibrations. This is then visible to you or anyone else who's also present in chat at the moment. The animations are also accompanied by vibrations.

Spiking bond yields driving sharp losses in tech stocks

A spike in interest rates since the start of the year has accelerated a rotation out of high-growth technology stocks and into value stocks poised to benefit from a reopening of the economy. The Nasdaq has fallen more than 10% over the past month as the Dow has soared to record highs, with a spike in the 10-year US Treasury yield acting as the main catalyst. It recently surged to a cycle high of more than 1.60% after starting the year below 1%. But according to Jim Paulsen, the Leuthold Group's chief investment strategist, rising interest rates do not represent a long-term threat to the stock market. Paulsen expects the 10-year yield to cross 2% by the end of the year. A spike in interest rates and its impact on the stock market depends on the economic backdrop, according to Paulsen. Rising interest rates amid a strengthening economy "may prove no challenge at all for stocks," Paulsen said.

ምን እንጠይቅሎ from ua


Telegram ምን እንጠይቅሎ?
FROM USA